የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በስሩ ካሉ ዳይሬክቶሬቶች ጋር የ2018 በጀት አመት ውጤት ተኮር እቅድ ላይ የግብ ስምምነት ተፈራረሙ ።

  • Post last modified:August 25, 2025

የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በስሩ ካሉ ሶስት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች ጋር የ2018 በጀት አመት ውጤት ተኮር እቅድ ላይ የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል ፡፡

አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ የግብ ስምምነት በተፈራረሙበት ወቅት እንደተናገሩት በተጠናቀቀዉ 2017 በጀት ዓመት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን ይበልጥ በማጎልበትና በ2018 በጀት ዓመት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አንስተዋል ።

የውጤት ተኮር እቅዱን የተፈራረሙት የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተ ምግብ አገልግሎት ፣ ዘርፈ ብዙ ኤችአይቪ ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር እንዲሁም በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዳይሬክቶሬቶች ናቸው ።

በሸምሲያ አደም