በ2017 በጀት ዓመት በአጠቃላይ የጤናው ዘርፍ አፈጻጸም በላቀ ለፈጸሙ የወረዳ እና ከተማ ጤና ጽ/ቤቶች እውቅና እና ሽልማት ተሰጠ ፡፡

  • Post last modified:October 5, 2025

በመግባባት ላይ የተመሰረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የጤና ቢሮ ጉባኤ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የወረዳ እና ከተማ ጤና ጽ/ቤቶች እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ፡፡

ከወረዳዎች መካከል አንደኛ ሶዶ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ፣ ሁለተኛ ምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ፣ እዣ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ወጥተዋል ፡፡

ከከተማ ጤና ጽ/ቤት መካከል አንደኛ ወልቂጤ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ፣ ሁለተኛ ቡታጅራ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ፣ እኩል ውጤት በማምጣት ሶስተኛ ደረጃ የወጡት ሆሳዕና እና ዱራሜ ከተማ ጤና ጽ/ቤቶች እውቅና እና ሽልማት በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ ሳህረላ አብዱላሂ ተበርክቶላቸዋል ፡፡